ኦሪት ዘዳግም Orit ZeDaGim
Deuteronomy / Devarim #23
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

ኦሪት ዘዳግም 23

Deuteronomy 23

1 ቍላው የተቀጠቀጠ ብልቱም የተቈረጠ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ።

1 He that is wounded in the stones, or hath his privy member cut off, shall not enter into the congregation of the Lord.

2 ዲቃላ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ እስከ አሥር ትውልድ ድረስ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ።

2 A bastard shall not enter into the congregation of the Lord; even to his tenth generation shall he not enter into the congregation of the Lord.

3-4 ከግብፅ በወጣችሁ ጊዜ እንጀራና ውኃ ይዘው በመንገድ ላይ አልተቀበሉአችሁምና፥ በመስጴጦምያ ካለው ከፋቱራ የቢዖርን ልጅ በለዓምን ዋጋ ሰጥተው ይረግምህ ዘንድ አምጥተውብሃልና አሞናዊና ሞዓባዊ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ እስከ አሥር ትውልድ ድረስ ለዘላለም ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ።

3 An Ammonite or Moabite shall not enter into the congregation of the Lord; even to their tenth generation shall they not enter into the congregation of the Lord for ever:
4 Because they met you not with bread and with water in the way, when ye came forth out of Egypt; and because they hired against thee Balaam the son of Beor of Pethor of Mesopotamia, to curse thee.

5 ነገር ግን አምላክህ እግዚአብሔር በለዓምን ይሰማ ዘንድ አልወደደም አምላክህም እግዚአብሔር ወድዶሃልና እርግማኑን በረከት አደረገልህ።

5 Nevertheless the Lord thy God would not hearken unto Balaam; but the Lord thy God turned the curse into a blessing unto thee, because the Lord thy God loved thee.

6 በዘመንህ ሁሉ ለዘላለም ሰላምና ልማት ለእነርሱ አትሻ።

6 Thou shalt not seek their peace nor their prosperity all thy days for ever.

7 ኤዶማዊው ወንድምህ ነውና አትጸየፈው ግብፃዊውንም በአገሩ ስደተኛ ነበርህና አትጸየፈው።

7 Thou shalt not abhor an Edomite; for he is thy brother: thou shalt not abhor an Egyptian; because thou wast a stranger in his land.

8 ከእነርሱም በሦስተኛው ትውልድ የሚወለዱ ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ ይግቡ።

8 The children that are begotten of them shall enter into the congregation of the Lord in their third generation.

9 ጠላቶችህን ልትወጋ በወጣህ ጊዜ ከክፉ ነገር ሁሉ ሰውነትህን ጠብቅ።

9 When the host goeth forth against thine enemies, then keep thee from every wicked thing.

10 በእናንተ መካከል ሌሊት በሚሆነው ርኵሰት የረከስ ሰው ቢኖር፥ ከሰፈር ወደ ውጭ ይውጣ፥ ወደ ሰፈርም አይግባ።

10 If there be among you any man, that is not clean by reason of uncleanness that chanceth him by night, then shall he go abroad out of the camp, he shall not come within the camp:

11 በመሸም ጊዜ በውኃ ይታጠብ ፀሐይም በገባ ጊዜ ወደ ሰፈር ይመለስ።

11 But it shall be, when evening cometh on, he shall wash himself with water: and when the sun is down, he shall come into the camp again.

12 ወደ ሜዳም ትወጣበት ዘንድ ከሰፈር ውጭ ቦታ ይሁንልህ።

12 Thou shalt have a place also without the camp, whither thou shalt go forth abroad:

13 ከመሣሪያህም ጋር መቈፈሪያ ያዝ በሜዳም በተቀመጥህ ጊዜ ትምስበታለህ፥ ዞረህም ከአንተ የወጣውን በአፈር ትከድነዋለህ።

13 And thou shalt have a paddle upon thy weapon; and it shall be, when thou wilt ease thyself abroad, thou shalt dig therewith, and shalt turn back and cover that which cometh from thee:

14 አምላክህ እግዚአብሔር ሊያድንህ ጠላቶችህንም በእጅህ አሳልፎ ሊሰጥ በሰፈርህ መካከል ይሄዳልና ስለዚህ ነውረኛ ነገር እንዳያይብህ፥ ፊቱንም ከአንተ እንዳይመልስ ሰፈርህ የተቀደስ ይሁን።

14 For the Lord thy God walketh in the midst of thy camp, to deliver thee, and to give up thine enemies before thee; therefore shall thy camp be holy: that he see no unclean thing in thee, and turn away from thee.

15 ከጌታው ኮብልሎ ወደ አንተ የመጣውን ባሪያ ለጌታው አሳልፈህ አትስጥ።

15 Thou shalt not deliver unto his master the servant which is escaped from his master unto thee:

16 ከደጆችህ በሚመርጣት በአንዲቱ በሚወድዳት ስፍራ ከአንተ ጋር በመካከልህ ይቀመጥ፥ አንተም አታስጨንቀው።

16 He shall dwell with thee, even among you, in that place which he shall choose in one of thy gates, where it liketh him best: thou shalt not oppress him.

17 ከእስራኤል ሴቶች ልጆች ሴት ጋለሞታ አትገኝ፥ ከእስራኤልም ወንዶች ልጆች ወንድ ጋለሞታ አይገኝ።

17 There shall be no whore of the daughters of Israel, nor a sodomite of the sons of Israel.

18 ስለ ተሳልኸው ስእለት ሁሉ የጋለሞታይቱን ዋጋና የውሻውን ዋጋ ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ቤት አታቅርብ ሁለቱም በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የሚያጸይፉ ናቸውና።

18 Thou shalt not bring the hire of a whore, or the price of a dog, into the house of the Lord thy God for any vow: for even both these are abomination unto the Lord thy God.

19 ለወንድምህ በወለድ አታበድር የብር ወይም የእህል ወይም የማናቸውንም ነገር ሁሉ ወለድ አትውሰድ።

19 Thou shalt not lend upon usury to thy brother; usury of money, usury of victuals, usury of any thing that is lent upon usury:

20 ለእንግዳው በወለድ አበድረው ነገር ግን አምላክህ እግዚአብሔር ልትወርሳት በምትገባባት ምድር በሥራህ ሁሉ ይባርክህ ዘንድ ለወንድምህ በወለድ አታበድር።

20 Unto a stranger thou mayest lend upon usury; but unto thy brother thou shalt not lend upon usury: that the Lord thy God may bless thee in all that thou settest thine hand to in the land whither thou goest to possess it.

21 ለአምላክህ ለእግዚአብሔር ስእለት በተሳልህ ጊዜ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ፈጽሞ ይሻዋልና፥ ኃጢአትም ይሆንብሃልና መክፈሉን አታዘገይ።

21 When thou shalt vow a vow unto the Lord thy God, thou shalt not slack to pay it: for the Lord thy God will surely require it of thee; and it would be sin in thee.

22 ባትሳል ግን ኃጢአት የለብህም።

22 But if thou shalt forbear to vow, it shall be no sin in thee.

23 በአፍህ የተናገርኸውን ለአምላክህ ለእግዚአብሔር በፈቃድህ ተስለሃልና ከከንፈርህ የወጣውን ታደርግ ዘንድ ጠብቅ።

23 That which is gone out of thy lips thou shalt keep and perform; even a freewill offering, according as thou hast vowed unto the Lord thy God, which thou hast promised with thy mouth.

24 ወደ ባልንጀራህ ወይን ቦታ በገባህ ጊዜ እስክትጠግብ ድረስ ከወይኑ ብላ ወደ ዕቃህ ግን ከእርሱ ምንም አታግባ።

24 When thou comest into thy neighbour’s vineyard, then thou mayest eat grapes thy fill at thine own pleasure; but thou shalt not put any in thy vessel.

25 ወደ ባልንጀራህ እርሻ በገባህ ጊዜ እሸቱን በእጅህ ቀጥፈህ ብላ ወዳልታጨደው ወደ ባልንጀራህ እህል ግን ማጭድ አታግባ።

25 When thou comest into the standing corn of thy neighbour, then thou mayest pluck the ears with thine hand; but thou shalt not move a sickle unto thy neighbour’s standing corn.