ኦሪት ዘፍጥረት Orit ZeFiTret
Genesis / Bereisheit #33
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

ኦሪት ዘፍጥረት 33

Genesis 33

1 ያዕቆብም ዓይኑን አነሣ፥ እነሆም ዔሳውን ሲመጣ አየው፥ ከእርሱም ጋር አራት መቶ ሰዎች ነበሩ ልጆቹንም ከፍሎ ወደ ልያና ወደ ራሔል ወደ ሁለቱም ባሪያዎች አደረጋቸው

1 And Jacob lifted up his eyes, and looked, and, behold, Esau came, and with him four hundred men. And he divided the children unto Leah, and unto Rachel, and unto the two handmaids.

2 ባሪያዎችንና ልጆቻቸውንም በፊት አደረገ፥ ልያንና ልጆችዋንም በኋለኛው ስፍራ፥ ራሔልንና ዮሴፍንም ከሁሉ በኋላ አደረገ።

2 And he put the handmaids and their children foremost, and Leah and her children after, and Rachel and Joseph hindermost.

3 እርሱም በፊታቸው አለፈ ወደ ወንድሙም እስኪደርስ ድረስ ወደ ምድር ሰባት ጊዜ ሰገደ።

3 And he passed over before them, and bowed himself to the ground seven times, until he came near to his brother.

4 ዔሳውም ሊገናኘው ሮጠ፥ አንገቱንም አቅፎ ሳመው ተላቀሱም።

4 And Esau ran to meet him, and embraced him, and fell on his neck, and kissed him: and they wept.

5 ዓይኑንም አነሣና ሴቶችንና ልጆችን አየ፥እንዲህም አለ፦ እነዚህ ምኖችህ ናቸው? እርሱም፦ እግዚአብሔር ለእኔ ለባሪያህ የሰጠኝ ልጆች ናቸው አለ።

5 And he lifted up his eyes, and saw the women and the children; and said, Who are those with thee? And he said, The children which God hath graciously given thy servant.

6 ሴቶች ባሪያዎችም ከልጆቻቸው ጋር ቀርበው ሰገዱ

6 Then the handmaidens came near, they and their children, and they bowed themselves.

7 ደግሞም ልያና ልጆችዋ ቀርበው ሰገዱ ከዚያም በኋላ ዮሴፍና ራሔል ቀርበው ሰገዱ።

7 And Leah also with her children came near, and bowed themselves: and after came Joseph near and Rachel, and they bowed themselves.

8 እርሱም፦ ያገኘሁት ይህ ሠራዊት ሁሉ ምንህ ነው? አለ። እርሱም፦ በጌታዬ ፊት ሞገስን አገኝ ዘንድ ነው አለ።

8 And he said, What meanest thou by all this drove which I met? And he said, These are to find grace in the sight of my lord.

9 ዔሳውም። ለእኔ ብዙ አለኝ ወንድሜ ሆይ፥ የአንተ ለአንተ ይሁን አለ።

9 And Esau said, I have enough, my brother; keep that thou hast unto thyself.

10 ያዕቆብም አለ። እንደዚህ አይደለም ነገር ግን በፊትህ ሞገስን አግኝቼ እንደ ሆንሁ እጅ መንሻዬን ተቀበለኝ የእግዚአብሔርን ፊት እንደሚያይ ፊትህን አይቼአለሁና፥ በቸርነትም ተቀብለኸኛልና።

10 And Jacob said, Nay, I pray thee, if now I have found grace in thy sight, then receive my present at my hand: for therefore I have seen thy face, as though I had seen the face of God, and thou wast pleased with me.

11 ይህችንም ያመጣሁልህን በረከቴን ተቀበል እግዚአብሔር በቸርነት ሰጥቶኛልና፥ ለእኔም ብዙ አለኝና። እስኪቀበለውም ድረስ ዘበዘበው።

11 Take, I pray thee, my blessing that is brought to thee; because God hath dealt graciously with me, and because I have enough. And he urged him, and he took it.

12 እርሱም፦ ተነሣና እንሂድ፥ እኔም በፊትህ እሄዳለሁ አለ።

12 And he said, Let us take our journey, and let us go, and I will go before thee.

13 እርሱም አለው፦ ጌታዬ ሆይ፥ ልጆቹ ደካሞች እንደ ሆኑ ታውቃለህ በጎችና ላሞችም ግልገሎቻቸውን ያጠባሉ ሰዎችም አንድ ቀን በችኮላ የነዱአቸው እንደ ሆነ ከብቶቹ ሁሉ ይሞታሉ።

13 And he said unto him, My lord knoweth that the children are tender, and the flocks and herds with young are with me: and if men should overdrive them one day, all the flock will die.

14 ጌታዬ ከባሪያው ፊት ቀድሞ ይለፍ እኔም ወደ ሴይር ከጌታዬ ዘንድ እስክደርስ ድረስ ከፊቴ ባሉት በእንስሳቱ እርምጃና በሕፃናቱ እርምጃ መጠን በዝግታ እከተላለሁ።

14 Let my lord, I pray thee, pass over before his servant: and I will lead on softly, according as the cattle that goeth before me and the children be able to endure, until I come unto my lord unto Seir.

15 ዔሳውም። ከእኔ ጋር ካሉት ሰዎች ከፍዬ ልተውልህን? አለ። እርሱም፦ ይህ ለምንድር ነው? በጌታዬ ዘንድ ሞገስን ማግኘት ይበቃኛል አለ።

15 And Esau said, Let me now leave with thee some of the folk that are with me. And he said, What needeth it? let me find grace in the sight of my lord.

16 ዔሳውም በዚያን ቀን ወደ ሴይር መንገዱን ተመለሰ።

16 So Esau returned that day on his way unto Seir.

17 ያዕቆብ ግን ወደ ሱኮት ሄደ በዚያም ለእርሱ ቤትን ሠራ፥ ለከብቶችም ዳሶችን አደረገ ስለዚህም የዚያን ቦታ ስም ሱኮት ብሎ ጠራው።

17 And Jacob journeyed to Succoth, and built him an house, and made booths for his cattle: therefore the name of the place is called Succoth.

18 ያዕቆብም ከሁለት ወንዞች መካከል በተመለሰ ጊዜ በከነዓን ምድር ወዳለችው ወደ ሴኬም ከተማ በደኅንነት መጣ በከተማይቱም ፊት ሰፈረ።

18 And Jacob came to Shalem, a city of Shechem, which is in the land of Canaan, when he came from Padan–aram; and pitched his tent before the city.

19 ድንኳኑን ተክሎበት የነበረውንም የእርሻውን ክፍል ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች በመቶ በጎች ገዛው።

19 And he bought a parcel of a field, where he had spread his tent, at the hand of the children of Hamor, Shechem’s father, for an hundred pieces of money.

20 በዚያም መሠውያውን አቆመ፥ ያንም ኤል ኤሎሄ እስራኤል ብሎ ጠራው።

20 And he erected there an altar, and called it El–elohe–Israel.