ኦሪት ዘኍልቍ Orit ZeHwilQwi
Numbers / Bamidbar #12
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

 

ኦሪት ዘኍልቍ 12

Numbers 12

1 ሙሴም ኢትዮጵያይቱን አግብቶአልና ባገባት በኢትዮጵያይቱ ምክንያት ማርያምና አሮን በእርሱ ላይ ተናገሩ።

1 And Miriam and Aaron spake against Moses because of the Ethiopian woman whom he had married: for he had married an Ethiopian woman.

2 እርሱም፦ በውኑ እግዚአብሔር በሙሴ ብቻ ተናግሮአልን? በእኛስ ደግሞ የተናገረ አይደለምን? አሉ እግዚአብሔርም ሰማ።

2 And they said, Hath the Lord indeed spoken only by Moses? hath he not spoken also by us? And the Lord heard it.

3 ሙሴም በምድር ላይ ካሉት ሰዎች ሁሉ ይልቅ እጅግ ትሑት ሰው ነበረ።

3 (Now the man Moses was very meek, above all the men which were upon the face of the earth.)

4 እግዚአብሔርም ወዲያው ሙሴንና አሮንን ማርያምንም። ሦስታችሁ ወደ መገኛኛው ድንኳን ውጡ ብሎ ተናገረ ሦስቱም ወጡ።

4 And the Lord spake suddenly unto Moses, and unto Aaron, and unto Miriam, Come out ye three unto the tabernacle of the congregation. And they three came out.

5 እግዚአብሔርም በደመና ዓምድ ወረደ፥ በድንኳኑም ደጃፍ ቆመ አሮንንና ማርያምን ጠራ፥ ሁለቱም ወጡ።

5 And the Lord came down in the pillar of the cloud, and stood in the door of the tabernacle, and called Aaron and Miriam: and they both came forth.

6 እርሱም፦ ቃሌን ስሙ በመካከላችሁ ነቢይ ቢኖር፥ እኔ እግዚአብሔር በራእይ እገለጥለታለሁ፥ ወይም በሕልም እናገረዋለሁ።

6 And he said, Hear now my words: If there be a prophet among you, I the Lord will make myself known unto him in a vision, and will speak unto him in a dream.

7 ባሪያዬ ሙሴ ግን እንዲህ አይደለም እርሱ በቤቴ ሁሉ የታመነ ነው።

7 My servant Moses is not so, who is faithful in all mine house.

8 እኔ አፍ ለአፍ በግልጥ እናገረዋለሁ፥ በምሳሌ አይደለም የእግዚአብሔርንም መልክ ያያል በባሪያዬ በሙሴ ላይ ትናገሩ ዘንድ ስለ ምን አልፈራችሁም? አለ።

8 With him will I speak mouth to mouth, even apparently, and not in dark speeches; and the similitude of the Lord shall he behold: wherefore then were ye not afraid to speak against my servant Moses?

9 እግዚአብሔርም ተቈጥቶባቸው ሄደ።

9 And the anger of the Lord was kindled against them; and he departed.

10 ደመናውም ከድንኳኑ ተነሣ እነሆም፥ ማርያም ለምጻም ሆነች፥ እንደ አመዳይም ነጭ ሆነች አሮንም ማርያምን ተመለከተ፥ እነሆም፥ ለምጻም ሆና ነበር።

10 And the cloud departed from off the tabernacle; and, behold, Miriam became leprous, white as snow: and Aaron looked upon Miriam, and, behold, she was leprous.

11 አሮንም ሙሴን፦ ጌታዬ ሆይ፥ ስንፍና አድርገናልና፥ በድለንማልና እባክህ፥ ኃጢአት አታድርግብ።

11 And Aaron said unto Moses, Alas, my lord, I beseech thee, lay not the sin upon us, wherein we have done foolishly, and wherein we have sinned.

12 ከእናቱ ሆድ በወጣ ጊዜ ግማሽ ሥጋው ተበልቶ እንደ ሞተ እርስዋ አትሁን።

12 Let her not be as one dead, of whom the flesh is half consumed when he cometh out of his mother’s womb.

13 ሙሴም ወደ እግዚአብሔር እየጮኸ። አቤቱ፥ እባክህ፥ አድናት አለው።

13 And Moses cried unto the Lord, saying, Heal her now, O God, I beseech thee.

14 እግዚአብሔርም ሙሴን፦ አባትዋ ምራቁን በፊትዋ ቢተፋባት ስንኳ ሰባት ቀን ታፍር ዘንድ ይገባት ነበር ሰባት ቀን ከሰፈር ውጭ ተዘግታ ትቀመጥ፥ ከዚያም በኋላ ትመለስ አለው።

14 And the Lord said unto Moses, If her father had but spit in her face, should she not be ashamed seven days? let her be shut out from the camp seven days, and after that let her be received in again.

15 ማርያምም ከሰፈር ውጭ ሰባት ቀን ተዘግታ ተቀመጠች ማርያምም እስክትመለስ ድረስ ሕዝቡ አልተጓዙም።

15 And Miriam was shut out from the camp seven days: and the people journeyed not till Miriam was brought in again.

16 ከዚያም በኋላ ሕዝቡ ከሐጼሮት ተጓዙ፥ በፋራንም ምድረ በዳ ሰፈሩ።

16 And afterward the people removed from Hazeroth, and pitched in the wilderness of Paran.