መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #120
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 120

Psalm 120

1 በተጨነቅሁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ ሰማኝም።

1 In my distress I cried unto the Lord, and he heard me.

2 ከዓመፀኛ ከንፈር ከሸንጋይም አንደበት፥ አቤቱ፥ ነፍሴን አድናት።

2 Deliver my soul, O Lord, from lying lips, and from a deceitful tongue.

3 ስለ ሽንገላ አንደበት ምንም ይሰጡሃል? ምንስ ይጨምሩልሃል?

3 What shall be given unto thee? or what shall be done unto thee, thou false tongue?

4 እንደ በረሃ እንጨት ፍም የኃያላን ፍላጾች የተሳሉ ናቸው።

4 Sharp arrows of the mighty, with coals of juniper.

5 መኖሪያዬ የራቀ እኔ ወዮልኝ በቄዳር ድንኳኖች አደርሁ።

5 Woe is me, that I sojourn in Mesech, that I dwell in the tents of Kedar!

6 ሰላምን ከሚጠሉ ጋር ነፍሴ ብዙ ጊዜ ኖረች።

6 My soul hath long dwelt with him that hateth peace.

7 እኔ ሰላማዊ ነኝ በተናገኋቸው ጊዜ ግን በከንቱ ተሰለፉብኝ።

7 I am for peace: but when I speak, they are for war.