መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #53
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 53

Psalm 53

1 ሰነፍ በልቡ። አምላክ የለም ይላል። ረከሱ በበደላቸውም ጐሰቈሉ በጎ ነገርን የሚያደርጋት የለም።

1 The fool hath said in his heart, There is no God. Corrupt are they, and have done abominable iniquity: there is none that doeth good.

2 የሚያስተውል እግዚአብሔርንም የሚፈልግ እንዳለ ያይ ዘንድ እግዚአብሔር ከሰማይ የሰው ልጆችን ተመለከተ።

2 God looked down from heaven upon the children of men, to see if there were any that did understand, that did seek God.

3 ሁሉ በደሉ፥ አብረውም ረከሱ አንድ ስንኳ በጎን ነገር የሚያደርጋት የለም።

3 Every one of them is gone back: they are altogether become filthy; there is none that doeth good, no, not one.

4 ሕዝቤን እንጀራ እንደሚበላ የሚበሉ ግፍ አድራጊዎች ሁሉ አያውቁምን? እግዚአብሔርንም አይጠሩትም።

4 Have the workers of iniquity no knowledge? who eat up my people as they eat bread: they have not called upon God.

5 እግዚአብሔር የግብዞችን አጥንቶች በትኖአልና። በዚያ የሚያስፈራ ሳይኖር እጅግ ፈሩ እግዚአብሔር ንቆአቸዋልና አሳፈርሃቸው።

5 There were they in great fear, where no fear was: for God hath scattered the bones of him that encampeth against thee: thou hast put them to shame, because God hath despised them.

6 መድኃኒትን ከጽዮን ለእስራኤል ማን በሰጠ! እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በመለሰ ጊዜ፥ ያዕቆብ ደስ ይለዋል እስራኤልም ሐሤት ያደርጋል።

6 Oh that the salvation of Israel were come out of Zion! When God bringeth back the captivity of his people, Jacob shall rejoice, and Israel shall be glad.