መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #73
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 73

Psalm 73

1 ልባቸው ለቀና ለእስራኤል እግዚአብሔር እንዴት ቸር ነው።

1 Truly God is good to Israel, even to such as are of a clean heart.

2 እኔ ግን እግሮቼ ሊሰናከሉ፥ አረማመዴም ሊወድቅ ትንሽ ቀረ።

2 But as for me, my feet were almost gone; my steps had well nigh slipped.

3 የኃጢአተኞችን ሰላም አይቼ በዓመፀኞች ቀንቼ ነበርና።

3 For I was envious at the foolish, when I saw the prosperity of the wicked.

4 ለሞታቸው መጣጣር የለውምና ኃይላቸውም ጠንካራ ነውና።

4 For there are no bands in their death: but their strength is firm.

5 እንደ ሰው በድካም አልሆኑም፥ ከሰው ጋርም አልተገረፉም።

5 They are not in trouble as other men; neither are they plagued like other men.

6 ስለዚህ ትዕቢት ያዛቸው ኃጢአትንና በደልን ተጐናጸፉአት።

6 Therefore pride compasseth them about as a chain; violence covereth them as a garment.

7 ዓይናቸው ስብ ስለ ሆነ ወጣ ልባቸውም ከምኞታቸው ይልቅ አገኘ።

7 Their eyes stand out with fatness: they have more than heart could wish.

8 አስበው ክፉ ነገርን ተናገሩ። ከፍ ከፍ ብለውም በዓመፃ ተናገሩ።

8 They are corrupt, and speak wickedly concerning oppression: they speak loftily.

9 አፋቸውን በሰማይ አኖሩ፥ አንደበታቸውም በምድር ውስጥ ተመላለሰ።

9 They set their mouth against the heavens, and their tongue walketh through the earth.

10 ስለዚህ ሕዝቤ ወደዚህ ይመለሳሉ ፍጹም ጊዜም በላያቸው ይገኛል

10 Therefore his people return hither: and waters of a full cup are wrung out to them.

11 እግዚአብሔር እንዴት ያውቃል? በልዑልስ ዘንድ በውኑ እውቀት አለ? ይላሉ።

11 And they say, How doth God know? and is there knowledge in the most High?

12 እነሆ፥ እነዚህ ኃጢአተኞች ይደሰታሉ፥ ሁልጊዜም ባለጠግነታቸውን ያበዛሉ።

12 Behold, these are the ungodly, who prosper in the world; they increase in riches.

13 እንዲህም አልሁ። በውኑ ልቤን በከንቱ አጸደቅሁ፥ እጆቼንም በንጽሕና በከንቱ አጠብሁ።

13 Verily I have cleansed my heart in vain, and washed my hands in innocency.

14 ሁልጊዜም የተገረፍሁ ሆንሁ፥ መሰደቤም በማለዳ ነው።

14 For all the day long have I been plagued, and chastened every morning.

15 እንደዚህ ብዬ ብናገር ኖሮ፥ እነሆ፥ የልጆችህን ትውልድ በበደልሁ ነበር።

15 If I say, I will speak thus; behold, I should offend against the generation of thy children.

16 አውቅም ዘንድ አሰብሁ፥ ይህ ግን በፊቴ ችግር ነበረ።

16 When I thought to know this, it was too painful for me;

17 ወደ እግዚአብሔር መቅደስ እስክገባ ድረስ፥ ፍጻሜአቸውንም እስካስተውል ድረስ።

17 Until I went into the sanctuary of God; then understood I their end.

18 በድጥ ስፍራ አስቀመጥኻቸው፥ ወደ ጥፋትም ጣልኻቸው።

18 Surely thou didst set them in slippery places: thou castedst them down into destruction.

19 እንዴት ለጥፋት ሆኑ! በድንገት አለቁ ስለ ኃጢአታቸውም ጠፉ።

19 How are they brought into desolation, as in a moment! they are utterly consumed with terrors.

20 ከሕልም እንደሚነቃ፥ አቤቱ፥ ስትነቃ ምልክታቸውን ታስነውራለህ።

20 As a dream when one awaketh; so, O Lord, when thou awakest, thou shalt despise their image.

21 ልቤ ነድዶአልና፥ ኵላሊቴም ቀልጦአልና

21 Thus my heart was grieved, and I was pricked in my reins.

22 እኔ የተናቅሁ ነኝ አላውቅሁምም፥ በአንተ ዘንድም እንደ እንስሳ ሆንሁ።

22 So foolish was I, and ignorant: I was as a beast before thee.

23 እኔ ግን ዘወትር ከአንተ ጋር ነኝ፥ ቀኝ እጄንም ያዝኸኝ።

23 Nevertheless I am continually with thee: thou hast holden me by my right hand.

24 በአንተ ምክር መራኸኝ ከክብር ጋር ተቀበልኸኝ።

24 Thou shalt guide me with thy counsel, and afterward receive me to glory.

25 በሰማይ ያለኝ ምንድር ነው? በምድርስ ውስጥ ከአንተ ዘንድ ምን እሻለሁ?

25 Whom have I in heaven but thee? and there is none upon earth that I desire beside thee.

26 የልቤ አምላክ ሆይ፥ ልቤና ሥጋዬ አለቀ እግዚአብሔር ግን ለዘላለም እድል ፈንታዬ ነው።

26 My flesh and my heart faileth: but God is the strength of my heart, and my portion for ever.

27 እነሆ፥ ከአንተ የሚርቁ ይጠፋሉና ከአንተ ርቀው የሚያመነዝሩትንም ሁሉ አጠፋኻቸው።

27 For, lo, they that are far from thee shall perish: thou hast destroyed all them that go a whoring from thee.

28 ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል መታመኛዬም እግዚአብሔር ነው በጽዮን ልጅ በሮች ምስጋናህን ሁሉ እናገር ዘንድ።

28 But it is good for me to draw near to God: I have put my trust in the Lord God, that I may declare all thy works.