መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David  #92
In Amharic and English

Can’t see Amharic font?

መዝሙረ ዳዊት 92

Psalm 92

1 እግዚአብሔርን ማመስገን መልካም ነው፥ ልዑል ሆይ፥ ለስምህም ዝማሬ ማቅረብ

1 It is a good thing to give thanks unto the Lord, and to sing praises unto thy name, O most High:

2 በማለዳ ምሕረትን፥ በሌሊትም እውነትህን ማውራት

2 To shew forth thy lovingkindness in the morning, and thy faithfulness every night,

3 አሥር አውታር ባለው በበገና፥ ከምስጋና ጋርም በመሰንቆ።

3 Upon an instrument of ten strings, and upon the psaltery; upon the harp with a solemn sound.

4 አቤቱ፥ በሥራህ ደስ አሰኝተኸኛልና በእጅህም ሥራ ደስ ይለኛልና።

4 For thou, Lord, hast made me glad through thy work: I will triumph in the works of thy hands.

5 አቤቱ፥ ሥራህ እጅግ ትልቅ ነው፥ አሳብህም እጅግ ጥልቅ ነው።

5 O Lord, how great are thy works! and thy thoughts are very deep.

6 ሰነፍ ሰው አያውቅም። ልብ የሌለውም ይህን አያስተውለውም።

6 A brutish man knoweth not; neither doth a fool understand this.

7 ኃጢአተኞች እንደ ሣር ሲበቅሉ ዓመፃ የሚያደርጉ ሁሉ ሲለመልሙ፥ ለዘላለም ዓለም እንዲጠፋ ነው።

7 When the wicked spring as the grass, and when all the workers of iniquity do flourish; it is that they shall be destroyed for ever:

8 አቤቱ፥ አንተ ግን ለዘላለም ልዑል ነህ

8 But thou, Lord, art most high for evermore.

9 አቤቱ፥ እነሆ፥ ጠላቶችህ ይጠፋሉና፥ ዓመፃንም የሚሠሩ ሁሉ ይበተናሉና።

9 For, lo, thine enemies, O Lord, for, lo, thine enemies shall perish; all the workers of iniquity shall be scattered.

10 ቀንዴ አንድ ቀንድ እንዳለው ከፍ ከፍ ይላል ሽምግልናዬም በዘይት ይለመልማል።

10 But my horn shalt thou exalt like the horn of an unicorn: I shall be anointed with fresh oil.

11 ዓይኔም በጠላቶቼ ላይ አየች፥ ጆሮዬም በእኔ ላይ በቆሙ በክፉዎች ላይ ሰማች።

11 Mine eye also shall see my desire on mine enemies, and mine ears shall hear my desire of the wicked that rise up against me.

12 ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል፥ እንደ ሊባኖስ ዝግባም ያድጋል።

12 The righteous shall flourish like the palm tree: he shall grow like a cedar in Lebanon.

13 በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ተተክለዋል፥ በአምላካችንም አደባባይ ውስጥ ይበቅላሉ።

13 Those that be planted in the house of the Lord shall flourish in the courts of our God.

14 ያን ጊዜ በለመለመ ሽምግልና ያፈራሉ ደስተኞችም ሆነው ይኖራሉ።

14 They shall still bring forth fruit in old age; they shall be fat and flourishing;

15 አምላኬ እግዚአብሔር እውነተኛ እንደ ሆነ ይነግራሉ፥ በእርሱም ዘንድ ዓመፃ የለም።

15 To shew that the Lord is upright: he is my rock, and there is no unrighteousness in him.